የአዳማ ሳይንሰና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ከሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር በመተባበር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስልጠና ሰጠ፡፡
አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አብረው መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ
የአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩንቨርስቲ ከስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ጋር የማማከር አገልግሎት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ
ASTU signs MoU with AMG steel factory
International Women's Day was celebrated at Adama Science and Technology University
ASTU commemorates World Water Day and the 13th anniversary of GERD

Capture1

የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፀረ - ሙስና ዳይሬክቶሬት ባዘጋጀው መድረክ “ ሙስና የጋራ ጠላታችን ነው በህብረት እንታገል “ በሚል መሪ ቃል 20ኛው አለም አቀፍ የፀረ- ሙስና ቀን የተመለከተ ዝግጅት ተካሂዷል ፡፡ በዝግጅቱ ላይተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ልማት ም/ፕሬዝዳንት ዶክተር ሰለሞን ጥሩነህ እንደገለፁት ሙስና አለም አቀፍና ድንበር ተሻጋሪ ችግር መሆኑን መገንዘብ እንደሚያስፈልግ ጠቁመው ፤ እንደ ሀገር ማህበረሰብንና ሀገርን የሚጎዳ ስለሆነ መፍትሄው በጋራ መታገልና አስተሳሰብን መቀየር ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
ዶክተር ሰለሞን አክለውም ራሳችን ተለውጠን ሌላውንም መለወጥ እንድንችል ሙስናን በጋራ በመታገል እና ሀገራችን ከሌላት ጊዜና ሀብት ላይ የሚጠፋውን በማስቀረት የነገውን ትውልድ ማዳን ይገባል በማለተት አክለዋል ፡፡
አቶ ባይሳ አያኖ የዩኒቨርሲቲዉ የፀረ - ሙስናና ስነምግባር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በበኩላቸው ሀገር አቀፍ የፀረ - ሙስና ወቅታዊ ቁመናና ትግል የሚያሳይ የመወያ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን በትንታኔያቸውም እንደገለፁት ኢትዮጵያ ታህሳስ 17 / 1993 ዓ.ም በሜክሲኮ ሜሪዳ ከተማ ሙስናን ለመከላከል የተፈረመውን አለም አቀፍ ኮንቬንሽን ከፈረሙ እና የህጋቸው አካል ካደረጉ 190 ሀገራት አንዷ መሆኗን አስታውሰዋል፡፡ በማብራሪያቸውም እንደጠቀሱት ሙስና ጥቂቶችን የሚያበለፅግ እና ብዙዎችን የሚጎዳ ችግር በመሆኑ የሀገርን ኢኮኖሚያዊ ፣ማህበራዊና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴን በማናጋት ሀገርን ሊበትን የሚችል ድንብር ተሸጋሪ ችግር መሆኑን ጠቁመው በ2013 የተካሄደው ጥናት እንደሚያመለክተው በኢትዮጵያ ከስራ አጥነትና ኑሮ ውድነት ቀጥሎ ሙስና 3ኛው ግዙፍ የሀገራችን ችግር መሆኑን ገለፀዋል ፡፡

በዝግጅቱ ከተሳታፊዎች በተነሱ ሀሳቦች ላይ ውይይት ተካሄዶዋል ፡፡

Media Gallery

  • 1.jpg
  • 1a.jpg
  • 2.jpg
  • 3.jpg
  • 3a.jpg
  • 3aa.jpg
  • 3b.jpg
  • 4.jpg
  • 5.jpg
  • 6.jpg
  • 7a.jpg
  • 8.jpg
  • 8a.jpg
  • 8aa.jpg
  • 8b.jpg
  • 8c.jpg
  • 8d.jpg
  • 8f.jpg
  • 8g.jpg
  • 8i.jpg
  • 8j.jpg
  • 9.jpg
  • 9a.jpg
  • 9aa.jpg
  • 9b.jpg
  • 9bb.jpg
  • 9c.jpg
  • 9d.jpg
  • 9f.jpg
  • 9g.jpg

ASTU Campuse Map

maps1

Contact us

International Relations and Corporate Communications
Office: +251 -22-211-3961,  Email: irccd@astu.edu.et
P.O.Box: 1888 Adama, Ethiopia
Office of Registrar  
Office: +251 -221-100001,  Email: sar@astu.edu.et
P.O.Box: 1888 Adama, Ethiopia


   © 2020  Adama Science and Technology University